የዓለምአቀፉ የቱሪስት አስጎብኚ ማኅበራት ፌዴሬሽን አባል የሆነው የኢትዮጵያ ቱሪስት አስጎብኚ ባለሙያዎች ማኅበር የቱሪስት አስጎብኚ አባላቱን ጤናውን በስፖርት እንዲጠብቅ በማሰብ ዘወትር ሐሙስ ከቀኑ 10:00-12:00 ሰዓት የእግር ኳስ ጨዋታ ለማድረግ በዛሬው ዕለት ማለትም የካቲት 28፣2016 ዓ.ም “የጤና ስፖርት ለአስጎብኚው ጤንነት” በሚል መርህ በይፋ አስጀምሯል። ሁሉም የማኅበራችን አባላት ለመጪው ሳምንት ተጋብዛችኋል።